ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር

ከሊቀ ልሣናት ቀሲስ ከፍያለው ጥላሁን

ሥነ ምግባር፡- ማለት ደግነት፣ በጎነት፣ መልካም ጠባይ ማለት ሲሆን ክርስቲያን የሚለው ቃል ሲጨመርበት ደግሞ የተሟላና የተለየ ያደርገዋል፡፡ መልካም ጠባይ ማንም ሰው ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የተሟላ ዘላቂና የሁል ጊዜ ሆኖም ለሰማያዊ መንግሥት የሚያበቃው በክርስትና እምነት ሲኖሩ ነው፡፡

ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር፡- በምድር እያለን ሰማያዊ ኑሮ ኖረን ለሰማያዊ መንግሥት የምንበቃበት ሕይወት ነው፡፡ ሰውን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ማስደሰት ነውና፡፡ በመሆኑም ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር በሚከተሉት ሕግጋት ሊለካ ይችላል፡፡

1.    ሕገ እግዚአብሔር

መጀመሪያውና ዋነኛው የክርስቲያን ሥነ ምግባር መለኪያው ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ አንድ ሰው ምናልባትም ሕይወቱ በሰው ፊት ሲታይ የማያስደስት በአፍአ ያለው ጠባዩ እንከን የማይወጣለት ሊሆን ይችላል፡፡ በሕገ እግዚአብሔር ተመዝኖ ካላለፈ ዋጋ የለውም በሰው ፊት መልካም ሆኖ የሚታይ ምግባር እግዚአብሔርን ሊያስደስት ያስፈልጋል፡፡ “የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ፡፡” ፌፌ.6፥6

Read more

መፃጉዕ (የዐቢይ ጾም አራተኛ ሳምንት)

 
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

አምላኩሰ ለአዳም ለዕረፍት ሰንበተ ሠርዓ ወይቤልዎ አይሁድ በዓይ ሥልጣን ትገብር ዘንተ ወይቤሎሙ ኢየሱስ አነኒ እገብር አንትሙኒ እመኑ ለግብርየ ወይቤሎሙ አነ ውእቱ እግዚኦ ለሰንበት እግዚኦ ውእቱ ለሰንበት ወልድ ዋሕድ ወይቤሎሙ ብውህ ሊተ እኅድግ ኃጢአተ በዲበ ምድር እስበክ ግዕዛነ ወእክሥት አዕይንተ ዕውራን አቡየ ፈነወኒ

ትርጉም: “የአዳም ፈጣሪ ለዕረፍት ሰንበትን ሠራ፤ አይሁድም በማን ሥልጣን ይህን ታደርጋለህ አሉት፤ እርሱም እኔ እሠራለሁ እናንተም ሥራዬን እመኑ አላቸው፡፡ የሰንበት ጌታው እኔ ነኝ፤ የሰንበት ጌታው/የአብ/ አንድያ ልጁ ነው፡፡ በምድር ላይ ኃጢአትን ይቅር እል ዘንድ ፣ ነፃነትን እሰብክ ዘንድ ተሰጥቶኛል ፣ የዕውራንን ዓይን አበራ ዘንድ አባቴ ልኮኛል አላቸው፡፡” ማለት ነው፡፡

Read more

አውደ ወራዙት (ወጣትነት በቤተክርስቲያን)

“ልጆቻችሁ በጐልማሳነታቸው እንደአትክልት አደጉ ፡፡ ሴቶች ልጆቻችሁም በግንብ ሥር እንዳለ አንደተወቀረ የማዕዘን ዐምድ ይሆኑ ዘንድ” መዝ.4 ፡ 02

ወጣትነት ምንድን ነው

ወጣትነት የሚለው ቃል ታላቅና ለጆሮ የሚያስደስት ቃል ነው፡፡ ወጣትነት በሰው ልጅ እድሜ ቀመር የእሳትነት ወቅት የሚባልው ሲሆን በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ከ15 እስከ 50 ወይም ከ20 እስከ 40 ዓመት ያለውን እድሜ ክልል ያጠቃልላል፡፡ በኢትጵያ ህግ መሠረት ደግሞ ከ 18 ዓመት በላይ ከ 40 ዓመት በታች ያለው የወጣትነት ዘመን ይባላል፡፡  ወጣቶች በአትክልት ውስጥ እንደሚገኙ አበቦችና እንደ ጥዋት ፀሐይ ጮራ ናቸው፡፡ የወጣትነት ዘመን በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ የተሻለው ተፈላጊ ምርጥ ጊዜ ነው፡፡

በሰው ልጆች ህይወት ውስጥ የጥፋት ጨለማ ተወግዶ ብርሃን፤ እንዲሁም ቁንጅናም ሊታይ – የሚችለው በወጣትነት ነው፡፡፡ የወጣትነት ዘመን ሰው እውነተኛ ጠባዩን ፤ባሕርዩንና ተግባሩን የሚገነባበት፤ በሰዓቱ የሚጠናቀቅበትና ሳይመለስ የሚያልፈው ደቂቃው እንዳያመልጠው የሚገነዘብበት ጊዜ ነው፡፡ ወጣቶች በጊዜያቸው ቢሠሩ ያከናውናሉ፤ ቢናገሩ ያሳምራሉ፤ ቢነሡ የጀመሩትን ዳር ያደርሳሉ፤ ቢጣሩ ይሰማሉ፡፡ ወጣቶች ቤተክርስቲያንና በጠቅላላ የሰዎች ልጆች ማኀበራዊ አቋሞች የሚደገፉባቸው አዕማድ ናቸው፡፡ ወጣቶች በአባቶቻቸው ሥፍራ የሚተኩ ቤተሰብን፤ ቤተክርስቲያንንና አገርን የሚዋጉትን ክፋቶች የሚቋቋሙ ጠንካራ ኃይላት ናቸው፡፡ ወጣቶች በህይወታቸው አስተዋዮች፣ ደፋሮችና  አሸናፊዎች፣ በውስጣቸው ዕውቀትን ብልሃትን ፍልስፍናን የያዙና፤ ስለ ደኀና ኑሮ በውስጣቸው የሚቃጠሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡

{flike}{plusone}

Read more

ጾምና ጥቅሙ

ከሊቀ ጉባዔ ቀለመወርቅ ውብነህ
ጾም ለተወሰነ ሰዓት ከሁሉም ምግብ መከልከል፣ ሁሉንም ምግብ መተው ሲሆን ለተወሰነ ቀናት ማለት የጾሙ ቀናት እስኪያልፍ ድረስ ከተወሰኑ ምግቦች መከልከል የተወሰኑ ምግቦችን መተው ነው፡፡ ይህም ጥሉላትን ፈጽሞ መተው፣ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ጾም ከጥሉላት ምግቦች መከልከል ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጆችን ከሚጎዳ ነገር ሁሉ መከልከልና ለሌሎች መልካም ሥራ መሥራትንም ይጨምራል፡፡

ጾም ከሃይማኖት ጋር ዘለዓለማዊ የሆነ ዝምድና እና ጥብቅ ቁርኝት አለው፡፡ ጾም የራሱ የሆነ ሕግጋትና ሥርዓት ስለአለው ጾም ለምን እንደሚጾም፣ ለማን እንደሚጾም፣ መቼ እንደሚጾም፣ እንዴት እንደሚገባና እንዴት እንደሚወጣ ለይቶ የሚያሳውቅ የራሱ የሆነ ሕግና ደንብ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ጾም በብሉይ ኪዳን ከፍተኛ ቦታ የነበረው ሲሆን፣ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ጋር በሚገናኙበት /ጊዜ/ ወራት እህልና ውኃ በአፋቸው አይገባም ነበር፡፡ /ዘፀ.34፥28/ በሰው ልጆች በደልና ኃጢአት ብዛት የታዘዘው የእግዚአብሔር መቅሠፍት /መዓት/ የሚመለሰው /የሚወገደው/ ሕዝቡ በጾምና በጸሎት ሲለምኑትና ሊማልዱት እንደነበር /ዮናስ.2፥7-10/ ተጠቅሶ ይገኛል፡፡እንደ ቅዱስ ጴጥሮስና እንደ ቆርኔሌዎስ ማለት ነው፡፡ /የሐ.ሥራ 10፥3-9 ለተወሰነ ሰዓትም ከቆዩ በኋላ ጿሚው የሚበላው ዳንኤል በጾመ ጊዜ እንዳደረገው ከቅባት ነጻ የሆነ ምግብ ነው፡፡ “በዚያን ወራት አኔ ዳንኤል ሦስት ሣምንት ሙሉ ሳዝን ነበርኩ፡፡ ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም፡፡ ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም፡፡ ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም ይላል፡፡ /ዳን.10፥2-3/

Read more